image
image
image
image
image

"በመትከል ማንሰራራት›" በሚል መሪ ቃል በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ በተገኙበት በልደታ ክ/ከተማ የችግኝ ተከላ መርሐ ግብር አካሄደ፡፡

ሀምሌ 7, 2018
በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጥራቱ በየነ እንደገለጹት አረንጓዴ አሻራ መካሄድ ከጀመረ ጀምሮ ሀገራችን በተለያዩ አረንጓዴ መስህቦች እየደመቀችና የአየር ንብረቷም እየተሻሻለ መምጣት ችሏል ያሉ ሲሆን ዘንድሮም በመትከል ማንሰራራት በሚል መሪ ቃል የጀመርነዉ ችግኝ መትከል ሁሉም ህብረተስብ በንቃት ሊሳተፍበትና የተከለዉን ችግኝም ሊንከባከበዉ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ችግኝ በመትከል ሁሉም ዜጋ አሻራዉን ማሳረፍ ይጠበቅበታል በማለት የተናገሩት ክቡር አቶ ጥራቱ በየነ የአየር ንብረት ለውጥ እንዲስተካከልና የምግብ ዋስትና እንዲረጋገጥ የአረንጓዴ ልማት ተግባራችን ማጠናከር የሁሉም ድርሻ ሊሆንም ይገባል ብለዋል፡፡ የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ አበባ እሸቴ በየአመቱ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ እንደ ክፍለ ከተማችን ዉብ ሳቢና ማራኪ አካባቢን መፍጠር እየታቻለነው። እንዲሁም ክበባዊ አየሩም እንዲስተካከል ችግኝ ተከላዉ የራሱ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነዉ ይህም ከከተማና እስከ ሀገር ጥሩ ገጽታና አዲስ አበባን እንደስሟ አበባ ማድረግ የተቻለበት አጋጣሚ ነዉ ያሉ ሲሆን የክፍለ ከተማችን ነዋሪዎች በእዚህ የአረንጓዴ አሻራ ትግበራ ላይ እያሳያችሁት ያለዉ ንቁ ተሳትፎ የሚበረታታ ነዉ ተጠናክሮ ሊቀጥልም ይገባል ብለዋል፡፡

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች