በልደታ ክ/ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ዋና ዋና አገልግሎቶች
- 1. በአካባቢ ብክለት እና ተጽእኖ ግምገማ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
- ስለአካባቢ ብክለት፣ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት
- ብክለት በሚያደርሱ ተቋማት ክትትልና ቁጥጥር ማድረግ ፣
- የብክለት መጠን በመለካት እርምጃ መውሰድ ፣
- የፕሮጀክቶችን የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ሰነዶችን በመገምገምና መቆጣጠር የማስተካከያ ሀሳብ መስጠት
- የአካባቢ አያያዝ ዕቅድ እና የአካባቢ ተፅእኖ ክዋኔ ሪፖርት መከታተል
- 2. በአየር ንብረት ለውጥ ቡድን የሚሰጡ ዋና ዋና አገልግሎቶች
- ስለአየር ንብረት ለውጥ፣ ህጎችና የአፈፃፀም መመሪያዎች ለህብረተሰቡ ስልጠናና ግንዛቤ መስጠት፣
- ለአየር ንብረት ለውጥን በዘርፍ መ/ቤቶች በዕቅድ መካተቱን ማረጋገጥ ፣
- ለአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ ተጋላጭ የህበረተስብ ክፍሎች ድጋፍና ክትትል ፣
- የኢነርጂ ቴክኖሎጂዎችን የዲዛይንና የፕሮሞሽን ስራ በመስራት ለተጠቃሚዎች ማስፋፋት፥
- 3. በስርዓተ ምህዳርና ብዝሃ ህይወት አጠቃቀም እና ቁጥጥር ቡድን ስር የሚሰጡ አገልግሎቶች
- በብዝሃ ህይወት ዙሪያ የተለያዩ የዳሰሳ ጥናቶችን መስራት እና ግኝታቸውን ለሚመለከተው አካል መላክ፤
- በአረንጓዴ ቦታዎች ላይ ሊፈጠሩ የሚችሉ፡ የእጽዋት፤ ተባዮች፣ በሽታዎች፣ የእሳት አደጋዎች፣ መጤና ወራሪ አረሞችን በሁሉም የአረንጓዴ ቦታዎች ላይ ክትትል እና ቁጥጥር በመስራት ግብረ መልስ ለሚመለከተው ሪፖርት ይልካል፤
- በአፈር መሸርሸር ምክንያት የተጎዳ ስርዓተ ምህዳርን በክትትል በመለየት ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ያደርጋል፤
- የችግኝ ጽድቀት መጠን ቆጠራ መስራት፤
- አረንጓዴ ቦታዎች በህገ ወጥ መንገድ ወረራ እንዳይፈፀምባቸው እና ለታለመላቸው ዓላማ ስለመዋላቸው ቁጥጥር እና ክትትል ማድረግ፤
- በአረንጓዴ መሰረተ ልማት እና ገፀ ምድር ማስዋብ ስራ ላይ መሰማራት ለሚፈልጉ እና ለሚያማክሩ በዘርፉ ለተመረቁ ባለሙያዎች የሙያ ፈቃድ መስጠት፤
- በሰው እና በዱር እንስሳት መካከል የሚነሳ ግጭትን ለማስቀረት የቅድመ ጥንቃቄ ትምህርት እና ግንዛቤ መስጠት፤
- ለሚቀርቡ የዛፍ ምልመላ እና ቆረጣ ጥያቄዎች ፍቃድ እንሰጣለን፤ (ይዞታ ካላቸው ግለሰቦች፣ ድርጅቶች፣ ማህበራት፣ ተቋማት… ጥያቄዎች ሲቀርቡ)፤
- ከሚቀርቡ የዛፍ ቆረጣ ፈቃድ የሮያሊቲ ገቢ መሰብሰብ፤
- የደን ውጤቶች የይለፍ ፈቃድ መስጠት፤